by Dawit Atreso
ሩሲያ ከዩክሬን ጋር ጦርነት ከገጠመች ወዲህ ባሉት የመጀመሪያዎቹ 100 ቀናት ወደ ውጭ ከላከችው ነዳጅ 98 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር ማግኘቷ ተመላከተ። የሩሲያን ነዳጅ በብዛት ከገዙ ሀገራት ውስጥ የአውሮፓ ሀገራት ቀዳሚውን ስፍራ መያዛቸውም ተነግሯል። የአውሮፓ ሀገራት ከሚያስፈልጋቸው የተፈጠሮ ጋዝ ውስጥ 40 በመቶውን ከሩሲያ የሚያገኙ ሲሆን፤ 27 በመቶ የነዳጅ ፎጆታቸውንም ከሩሲያ በሚያስገቡት ነው የሚሸፍኑት።